2013 ኖቬምበር 9, ቅዳሜ

በገለልተኛ አስተዳደር ስር የሚኖሩትን አጥቢያዎች ቁጥር በአንድ እንደሚቀንስ ይጠበቃል

  • ‹‹እግዚአብሔር ቅዱስ ፍቃዱ  ሆኖ ወደ ህብረትና አንድነታችን አንደምንመለስ ትልቅ ተስፋ ነው ያለኝ፡፡›› ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ከ12 ዓመት በፊት ካደረጉት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ

(አንድ አድርገን ጥቅምት 29 2006 ዓ.ም)፡- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ለሁለት አስርተ ዓመታት ወደኖሩበት አሜሪካ ጥቅምት 27 2006 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ በዘመነ ፕትርክናቸው እንደሚሄዱ ሰሞኑን ከተለያዩ ዜና ማሰራጫዎች ለመረዳት ችለናል። በመረጃው መሰረት ብፁዕነታቸው 6ተኛ ፓትርያርክ ተብለው ከተሸሙ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅምት 27 ወደ አሜሪካ አቅንተዋል ፡፡ ከብፁዕነታቸው ጋር ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኄኖክ እና ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ አብረዋቸው እንደተጓዙ ታውቋል ፡፡አካሄዳቸው በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘውን የመድኅኒዓለም ቤተክርስቲያን የቅዳሴ ቤት ለማክበር እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል።


እንደሚታወቀው ይህ አጥቢያ በብፁዕነታቸው ከተመሰረተ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስገለልተኛበሚባል አስተዳደር መቆየቱም ይታወሳል። በዚህ ታሪካዊ የብፁዕነታቸው ጉዞም ይህንን አጥቢያ ወደ እናት ቤተክርስቲያን አስተዳደር እንደሚመልሱት እና በቀጥታ በቅዱስ ሲኖዶስ በሚሾመው ሊቀ ጳጳስ እንደሚተዳደር ይጠበቃል። በዚህም በዋሺንግተን ዲሲ አካባቢ በገለልተኛ አስተዳደር ስር የሚኖሩትን አጥቢያዎች ቁጥር በአንድ እንደሚቀንስ እና መልካም እርምጃ እንደሚሆን ይጠበቃል። ሌሎችስ በአሜሪካ እና በተለያዩ የአውሮፓ ምድር ራሳቸውን ገለልተኛ ብለው የሚገኙ የአብያ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች ምን ይማሩ ይሆን? ከዚች ከአንዲት ቤተክርስቲያን ተገሎ እስከመቼ ይኖራል? እንደ ብዙዎች ምዕመናን አስተያየት ወደፊት እግዚአብሔር በፈቀደው ቀን በውጭ ሀገር የተመሰረተው ሲኖዶስ ከአዲስ አበባው ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር እንደሚቀላቀል እና አንድ እንደሚሆን እምነታው ነው ፤ የዛኔ ደግሞ አሁን ላይ ራሳቸውን ገለልተኛ ብለው የተቀመጡት ሌላ ፈተና ይሆናሉ ብለው ሃሳባቸውን ይገልጻሉ ፡፡ ዛሬም በነ አቶ ወይም ዶክተር እከሌ መመራት ወይስ ቀደምት አባቶቻችን በሰሩልን ሥርዓት መቀጠል? እኛ እኮ አባቶቻችን የሰሩልን የእምነት ስርዓት አስቀጣይ እንጂ እንደ አዲስ ጀማሪ መሆን መቻል የለብንም………ይህ መልካም ጅምር ነው ! ቸር ያሰማን

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...