ልጥፎችን በመለያ ጉዞና ትዝታዎች በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ልጥፎችን በመለያ ጉዞና ትዝታዎች በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ

2014 ጁን 26, ሐሙስ

የደብረ ሊባኖስ ገዳም አምስቱ ስያሜዎች




 ሰኔ 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
የደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም ገዳማዊ ሥርዓቱ እንደተጠበቀ ቢሆንም የጎርፍ አደጋ፤ የብዝኅ ሕይወት መመናመን፤ የሕገ ወጥ የመሬት ወረራና ሌሎችም ችግሮች እየተፈታተኑት ይገኛል፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት በገዳሙና በማኅበረ ቅዱሳን ባለሙያዎች ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ወደ ሥራ ተገብቷ



ፕሮጀክቶቹንም በተያዘላቸው እቅድ መሠረት ለማስፈጸም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሠኔ 8 ቀን 2006 ዓ.ም. የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ላይ ፕሮጀክቶቹንና ገዳሙን አስመልክቶ የተዘጋጀ መጽሔት ለምእመናን ተሰራጭቷል፡፡ ከመጽሔቱ ያገኘናቸውን ጥቂት መረጃዎች እናካፍላችሁ፡



Dedication of the Debre Libanos Church, November 18, 1962የደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃማኖት አንድነት ገዳም በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደር- ጎጃም መውጫ በ104 ኪሎ ሜትር ርቀት፤ ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ 4.5 ኪሎ ሜትር ተገንጥሎ የሚገኝ የአንድነት ገዳም ነው፡፡
ገዳሙ በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በ1296 ዓ.ም. የተቆረቆረ ሲሆን፤ 710 ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ በገዳሙ አስተዳደር ሥር ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በተጨማሪ የቅዱስ አማኑኤል እና የቅዱስ ፊልጶስ አብያተ ክርስቲያናት ይገኛሉ፡፡

በገዳሙ ውስጥ የሚጎበኙ የተለያዩ የነገሥታት ሥጦታዎች፤ ቅዱሳት መጻሕፍት፤ ንዋየ ቅድሳት፤ የቅዱሳን አጽም፤ ፈውስ የሚገኝባቸው የጸበል ቦታዎችም ይገኛሉ፡፡

የደብረ ሊባኖስ ገዳም አምስቱ ስያሜዎችን ስንመለከት፡-

ምድረ ግራሪያ፡-
ግራሪያ የሚለውን ስያሜ የሰጠችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ምድረ ግብጽ ስትሰደድ በኢትዮጵያ ውስጥ ከቆየችባቸው ቦታዎች አንዱ ይህ ቅዱስ ቦታ ነው፡፡ ለአንድ ሳምንት ቆይታ አድርጋ የቦታውን ስም ምድረ ግራሪያ ስትል ሰይማዋለች፡፡ ግራሪያ ማለት ኩሉ ይገርር ሎቱ፤ ሁሉ ይገዛላታል ማለት ነው፡፡ አንድም ግራር በቁሙ ለሁሉ ጥላ፤ መሰብሰቢያ እንደሆነ ደብረ ሊባኖስም የሁሉ ጥላ መሰብሰቢያ ነውና ምድረ ግራሪያ ተብሏል፡፡

2013 ኦክቶበር 10, ሐሙስ

ሰንበት ት/ቤቱ የካህናት  ሥልጠና አዘጋጀ
   በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ  ደብር የካህናት ሥልጠና ተዘጋጀ
የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ያዘጋጀው ይህ ሥልጠና ከመስከረም 20-28  /2006  ዓ.ም ነው ፡፡ በሥልጠናውም ትምህርተ  ኖሎት ፤ ሥርዓተ ቤተክረስቲያን 
  ክርሥቲያናዊ ሥነ ምግባር ፤ የግጭት አፈታት ዘዴ እና ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይች  በሥልጠናው ተካተዋል  የደብሩ ሰንበት ት/ቤት  በተለይ ለካህናቱ ስልጠና ማዘጋጀቱ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በተቀላጠፈ መልኩ ለመፈጸም ይረዳናል ያሉት ሠልጣኞች ካህናት ሥልጠናው ወደፊትም መቀጠል እንዳለበት ተቁመዋል፡፡ በተለይ አሁን ያለውን ትውልድ በሚገባ ለማገልገልና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለሕዝበ ክርስቲያኑ ለማድረስ ይቻል ዘንደ የካህናት ሥልጠና በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንደሚያስፈልግ የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ጠቁሞአል ፤በየደብሩ ይህ ተሞክሮ መቀጠል እንዳለበትም  የተጠቆመ ሲሆን ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በሚችሉት ሁሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ  ሰንበት ት/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡  በሰንበት ት/ቤቱ  የሚያገለግሉ ወጣቶች በየመሥሪያ ቤቱ የሚሰሩ ዲያቆናት ሌሎቹንም በማስተባበር ሥልጠናው የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋአል፡፡   

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...